Telegram Group & Telegram Channel
የሕይወት ሥነ ሥርዓት (16)

13- ንግግርህ ብቁ ይሁን

የሰው ልጅ ከእንስሳ የሚለየው አሳቢ ፣ ተናጋሪና ሕያው ፍጡር በመሆኑ ነው ። ጨርሶ አለመናገር ዱዳነት ፣ ያለ ዕረፍት መናገርም የተከፈተ መቃ መሆን ነው ። ዝም ያለ ሁሉ ጨዋ አይደለም ። የሚናገረው እውቀት የሌለው ሰው ዝም ይላል ። አውሬም ሲያደፍጥ ዝምታ ገንዘቡ ነው ። ስለሌላው አያገባኝም ብሎ የሚያስብ ሰው ዝም ይላል ። የርኅራኄ ወሬ የተነሣ እንደሆነ በሌላ ወሬ ያስቀይሰዋል ። የዘመኑ ወንጌል አማኝ ነን ባዮች ክፉ አትስማ በሚል መርሕ የሰው ችግር ሲሰሙ ውስጣዊ ጆሮአቸውን ይደፍናሉ ። ላለመራራት ይጠነቀቃሉ ። ብዙ ሰው ለእውነት ዝም ብሎ ለሣንቲም ይለፈልፋል ። አገር ሲወድም ዝም ብሎ ትዳሩ ሲናጋ “ሕዝብ ይፍረደኝ” ይላል ። ዝም ያለ ሁሉ አዋቂ አይደለም ። “አደራህን ንግግርህ አይጥምምና እንዳትናገር” ተብሎ በማስጠንቀቂያ የወጣ ዝም ይላል ። “አንገት ደፊ አገር አጥፊ” እንዲሉ ዝም የሚሉ ሰዎች በተንኮልና በመግደል ይናገራሉ ።

እግዚአብሔርን ለማዳመጥ ፣ የማዳኑን ቀን በተስፋ ለመጠበቅ ዝም የሚሉ አሉ ። “ብናገር ሰው ይቀየመኛል ፤ ዝም ብል እግዚአብሔር ያዝንብኛል” ብለው በመወላወል ዝም የሚሉ አሉ ። ቅዱስ ለመባል የቲያትር ዝምታ የሚለማመዱ ፣ “እርሱ እኮ ደርባባ አቡን” ይመስላል ለመባል ዝም የሚሉ ግብዞች አሉ ። ጢም አቡን ፣ ዝምታ ሊቅ አያደርግም ። መናገራቸው ለውጥ ስላላመጣ ትዳራቸው እየታወከ ፣ ልጆቻቸው አብዮት እያካሄዱባቸው ዝም የሚሉ አሉ ። ከመከራ የተነሣ ደንዝዘው “በማላውቀው ቀንና ሕይወት ውስጥ ነው የምኖረው” ብለው ዝም የሚሉ አሉ ። ዘረኞችም የአገሬ ሰው የሚሉት ሰው እስኪመጣ ዝም ይላሉ ፣ ከዚያ በኋላ የዘመኑ ልሳን ያቀልጡታል ። የሚገርመው ዘረኞችን እኛው ከወንዛቸው ልጅ አስተዋውቀናቸው በቋንቋቸው መናገር ጀምረው ይርሱናል ፣ ቀጥሎ ዘመዴ እኮ ነው ብለው የአክስት ልጅ መሆናቸውን ይነግሩናል ። ዘረኞች የሚዋደዱት የሚጠሉት ወገን እስኪጠፋ ድረስ ነው ። ዘረኞች ጭንቅላታቸውን ቆሻሻ መድፊያ ያደረጉ ፣ የፖለቲከኞች ቅርጫት ናቸው ።

የሚፈልጉትን ነገር ለማግኘት ዝምታን እንደ መሣሪያ የሚጠቀሙ የአዋቂ ሕፃናት ብዙ ናቸው ። እነዚህ ሰዎች አስፈራርተው ገንዘብ ከሚቀበሉ ዘራፊዎች የሚለዩ አይደሉም ። ቁሳዊ ፍላጎታቸውን ለማሟላት የሰውን የሕሊና ሰላም ይሰርቃሉ ። ተለዋዋጭ ስሜት ያላቸው ፣ አንዴ ሳቂታ አንዴ አኩራፊ የሚሆኑ ሰዎች ከመሬት ተነሥተው ዝም ይላሉ ። እነዚህ ሰዎች አውቆ አበድ ናቸው ። ቋሚ ማንነትም ስለሌላቸው ከተወሰነ ጊዜ በኋላ ሰው አልባ ይሆናሉ ። አዎ ዝምታው አንድ ዓይነት ነው ፣ ምክንያቱ ግን ብዙ ነው ።

ተናጋሪ ሰውም ሊቅ ወይም የዋህ አይደለም ። አንዳንድ ሰዎች ጆሮ ጠገብ ስለሆኑ የሰሙትን እንደ መቅረፀ ድምፅ ደግመው የመናገር ብቃት አላቸው ። “እገሌ ቢናገርም ሆዱ ባዶ ነው” ይባልላቸዋል ። እነርሱም “አንዴ ከተናገርኩ በኋላ በውስጤ ምንም አልይዝም” ይላሉ ። ጥይትም ከተተኮሰ በኋላ ቀለሃው ባዶ ነው ። ተናግረውም እንደገና በተግባር የሚበድሉ ድርብ በደለኞችና በቀለኞች አሉ ። ብቻ የሰው ክብሩ ዝምታውና መናገሩ ሳይሆን የት እንደሚናገር ማወቁ ነው ።

አንተ ግን ንግግርህ ቀና እንዲሆን ከሠላሳ በላይ ነጥቦች ተቀምጠዋል ተከተል፦ ከታገሥህ ቶሎ ቶሎ ለማቅረብ እንሞክራለን ።

ይቀጥላል

ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
ሚያዝያ 21 ቀን 2016 ዓ.ም.



tg-me.com/Nolawii/3925
Create:
Last Update:

የሕይወት ሥነ ሥርዓት (16)

13- ንግግርህ ብቁ ይሁን

የሰው ልጅ ከእንስሳ የሚለየው አሳቢ ፣ ተናጋሪና ሕያው ፍጡር በመሆኑ ነው ። ጨርሶ አለመናገር ዱዳነት ፣ ያለ ዕረፍት መናገርም የተከፈተ መቃ መሆን ነው ። ዝም ያለ ሁሉ ጨዋ አይደለም ። የሚናገረው እውቀት የሌለው ሰው ዝም ይላል ። አውሬም ሲያደፍጥ ዝምታ ገንዘቡ ነው ። ስለሌላው አያገባኝም ብሎ የሚያስብ ሰው ዝም ይላል ። የርኅራኄ ወሬ የተነሣ እንደሆነ በሌላ ወሬ ያስቀይሰዋል ። የዘመኑ ወንጌል አማኝ ነን ባዮች ክፉ አትስማ በሚል መርሕ የሰው ችግር ሲሰሙ ውስጣዊ ጆሮአቸውን ይደፍናሉ ። ላለመራራት ይጠነቀቃሉ ። ብዙ ሰው ለእውነት ዝም ብሎ ለሣንቲም ይለፈልፋል ። አገር ሲወድም ዝም ብሎ ትዳሩ ሲናጋ “ሕዝብ ይፍረደኝ” ይላል ። ዝም ያለ ሁሉ አዋቂ አይደለም ። “አደራህን ንግግርህ አይጥምምና እንዳትናገር” ተብሎ በማስጠንቀቂያ የወጣ ዝም ይላል ። “አንገት ደፊ አገር አጥፊ” እንዲሉ ዝም የሚሉ ሰዎች በተንኮልና በመግደል ይናገራሉ ።

እግዚአብሔርን ለማዳመጥ ፣ የማዳኑን ቀን በተስፋ ለመጠበቅ ዝም የሚሉ አሉ ። “ብናገር ሰው ይቀየመኛል ፤ ዝም ብል እግዚአብሔር ያዝንብኛል” ብለው በመወላወል ዝም የሚሉ አሉ ። ቅዱስ ለመባል የቲያትር ዝምታ የሚለማመዱ ፣ “እርሱ እኮ ደርባባ አቡን” ይመስላል ለመባል ዝም የሚሉ ግብዞች አሉ ። ጢም አቡን ፣ ዝምታ ሊቅ አያደርግም ። መናገራቸው ለውጥ ስላላመጣ ትዳራቸው እየታወከ ፣ ልጆቻቸው አብዮት እያካሄዱባቸው ዝም የሚሉ አሉ ። ከመከራ የተነሣ ደንዝዘው “በማላውቀው ቀንና ሕይወት ውስጥ ነው የምኖረው” ብለው ዝም የሚሉ አሉ ። ዘረኞችም የአገሬ ሰው የሚሉት ሰው እስኪመጣ ዝም ይላሉ ፣ ከዚያ በኋላ የዘመኑ ልሳን ያቀልጡታል ። የሚገርመው ዘረኞችን እኛው ከወንዛቸው ልጅ አስተዋውቀናቸው በቋንቋቸው መናገር ጀምረው ይርሱናል ፣ ቀጥሎ ዘመዴ እኮ ነው ብለው የአክስት ልጅ መሆናቸውን ይነግሩናል ። ዘረኞች የሚዋደዱት የሚጠሉት ወገን እስኪጠፋ ድረስ ነው ። ዘረኞች ጭንቅላታቸውን ቆሻሻ መድፊያ ያደረጉ ፣ የፖለቲከኞች ቅርጫት ናቸው ።

የሚፈልጉትን ነገር ለማግኘት ዝምታን እንደ መሣሪያ የሚጠቀሙ የአዋቂ ሕፃናት ብዙ ናቸው ። እነዚህ ሰዎች አስፈራርተው ገንዘብ ከሚቀበሉ ዘራፊዎች የሚለዩ አይደሉም ። ቁሳዊ ፍላጎታቸውን ለማሟላት የሰውን የሕሊና ሰላም ይሰርቃሉ ። ተለዋዋጭ ስሜት ያላቸው ፣ አንዴ ሳቂታ አንዴ አኩራፊ የሚሆኑ ሰዎች ከመሬት ተነሥተው ዝም ይላሉ ። እነዚህ ሰዎች አውቆ አበድ ናቸው ። ቋሚ ማንነትም ስለሌላቸው ከተወሰነ ጊዜ በኋላ ሰው አልባ ይሆናሉ ። አዎ ዝምታው አንድ ዓይነት ነው ፣ ምክንያቱ ግን ብዙ ነው ።

ተናጋሪ ሰውም ሊቅ ወይም የዋህ አይደለም ። አንዳንድ ሰዎች ጆሮ ጠገብ ስለሆኑ የሰሙትን እንደ መቅረፀ ድምፅ ደግመው የመናገር ብቃት አላቸው ። “እገሌ ቢናገርም ሆዱ ባዶ ነው” ይባልላቸዋል ። እነርሱም “አንዴ ከተናገርኩ በኋላ በውስጤ ምንም አልይዝም” ይላሉ ። ጥይትም ከተተኮሰ በኋላ ቀለሃው ባዶ ነው ። ተናግረውም እንደገና በተግባር የሚበድሉ ድርብ በደለኞችና በቀለኞች አሉ ። ብቻ የሰው ክብሩ ዝምታውና መናገሩ ሳይሆን የት እንደሚናገር ማወቁ ነው ።

አንተ ግን ንግግርህ ቀና እንዲሆን ከሠላሳ በላይ ነጥቦች ተቀምጠዋል ተከተል፦ ከታገሥህ ቶሎ ቶሎ ለማቅረብ እንሞክራለን ።

ይቀጥላል

ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
ሚያዝያ 21 ቀን 2016 ዓ.ም.

BY Nolawi ኖላዊ


Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 283

Share with your friend now:
tg-me.com/Nolawii/3925

View MORE
Open in Telegram


Nolawi ኖላዊ Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

The messaging service and social-media platform owes creditors roughly $700 million by the end of April, according to people briefed on the company’s plans and loan documents viewed by The Wall Street Journal. At the same time, Telegram Group Inc. must cover rising equipment and bandwidth expenses because of its rapid growth, despite going years without attempting to generate revenue.

For some time, Mr. Durov and a few dozen staffers had no fixed headquarters, but rather traveled the world, setting up shop in one city after another, he told the Journal in 2016. The company now has its operational base in Dubai, though it says it doesn’t keep servers there.Mr. Durov maintains a yearslong friendship from his VK days with actor and tech investor Jared Leto, with whom he shares an ascetic lifestyle that eschews meat and alcohol.

Nolawi ኖላዊ from tw


Telegram Nolawi ኖላዊ
FROM USA